ብልጽግና የሀገራችን ህዝቦች የመዳረሻ ምዕራፍ እንዲሆን በፓርቲያችን አመራሮች እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ይበል የሚያሰኙ ናቸው፡፡ በተለይ ደግሞ የህዝቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥና የእለተ እለት ህይወቱን በመቀየር ረገድ እየተከፈሉ ያሉ መስዋእተነቶች ለመዳረሻው ምቹ ሁኔታን የሚፈጥሩ ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ ይሁን እንጂ ብልጽግናችንን የሚገዳደሩ ሰንኮፎች እዚህም እዚም ብቅ ብቅ ማለታቸው አሁንም ቢሆን አልቀረም፡፡ እንደ ክፍለ ከተማችንም ከእነዚህ ሰንኮፎች መካከል አንዱ የሆነው ህገ ወጥነት ባለ መልከ ብዙ ሆኖ ከጀመርነው አገራዊ ጉዞ ሊያደናቅፈን እየታገለን ይገኛል፡፡ አመራራችንና የክፍለ ከተማችን ነዋሪም ይህን ሰንኮፍ በመንቀል ብልጽግናን ለማረጋገት በጋራ እየዘመተ ውጤትም እየተገኘ ነው፡፡ የህዝብን ምሬት የሚጨምሩና በጉሮሮው ላይ የሚቆሙ ህገ ወጥነቶችንም ተከታትሎ አደብ በማስያዝ ላይ ይገኛል፡፡ በክፍለ ከተማችን ወረዳ 12 በህገወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘ 6ሺህ 600 ካርቶን (132ሺህ ሊትር) የምግብ ዘይት በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል። ለክፍለ ከተማችን ነዋሪዎችና የየፀጥታ ሀይሎች ከአመራሮቻችን ጋር በመቀናጀት ህገወጦችን ለማጋለጥ ላደረጋችሁት ክትትልና ቁጥጥር የሚመሠገን ሲሆን በህገወጥ ተግባራት ላይ የተሰማሩ አካላትን የማጋለጡ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ተግባር እንደሆነም ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡

‹‹ህገ ወጥነት የብልጽግናችን ሰንኮፍ በመሆኑ እንንቀለው!!››
- Post author:admin
- Post category:ዜና
- Post last modified:February 19, 2021
- Post published:February 19, 2021
- Post comments:0 Comments
- Reading time:0 mins read
እባክዎን ይህንን ያጋሩ Share this content
You Might Also Like

‹‹ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ለብልጽግና ጉዟችን ስኬት እናውለው!››

‹‹የኢትዮጵያውያን ሀብት የአፍሪካውያን ኩራት አድዋ!››

‹‹የፓርቲና የመንግስት ስራዎቻችን በጠንካራ የህዝብ ግንኙነት ይታጀቡ!››

‹‹የወጣቶቻችንን ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ለማረጋገጥ እንተጋለን!››

‹‹ህዳርን እናጥናለን፤ጁንታውንም በማስወገድ የትግራይንና የኢትዮጵያን ህዝቦች ነጻ እናወጣለን!››

‹‹ወቅቱ በርካታ ችግሮችን የምንዘረዝርበት ሳይሆን አንዲት ፍሬ መፍትሔ የምናበረክትበት ይሁን!››

‹‹የይቻላል መንፈስን በመላበስ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን እንቅረፍ››

‹‹መንደርን ማዕከል ያደረገ የብሎክ አደረጃጀት ለሰላምና ለልማት››
