በክ/ከተማችን ሴቶች ብሔራዊ አንድነታቸውን ጠብቀው የመተሳሰብና የመረዳዳት ባህል ማጎልበት በሀገራዊ ጉዳዮች ገንቢ ሚና እንድጫወቱ መስራት፡፡
በፓርቲዉና በሴቶቹ መሃል መሸጋገሪያ ድልድይ በመሆን ቀጣይ ሃገር ተረካቢ ትውልድ መፍጠር የብልፅግና አላማ እና ህልውና በቀጣይነት ማረጋገጥ፡፡
በክ/ከተማችን ሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማረጋገጥ በብልፅግና አላማዎች ዙሪያ የተሰባሰቡ ሴቶች የመታገያ መድረክ ሆኖ ማገልገል፡፡
- የብልፅግና ፓርቲ ፕሮግራም በህዝቡ ውስጥ ሰርፆ ጠንካራ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ቅቡልነት ያለው፣ ዘላቂ ሀገረ መንግሥት ግንባታ በስራ እንድተረጎም እና በዘላቂነት የወጣቶች ፍትሃዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ መስራት፡፡
- በክ/ከተማችንን ሴቶች ሁለንተናዊ ብልፅግናን የሚያሰፍን ማኅበራዊ ልማት እንዲረጋገጥ ማስቻል እና የብልፅግና አላማዎችን ለማሳካት መታገል፡፡
- በክ/ከተማችን ሴቶች በአስተሳሰብና በተግባር አለም ከደረሰበት የፖለቲካ ኢኮኖሚ ብልፅግና ደረጃ ላይ እንዲደርሱ መስራት፡፡