ወጣቶች የዛሬዋና የነገዋ ኢትዮጵያ ተረካቢ ብቻ ሳይሆኑ ዋልታና ማገርም ናቸው፡፡ ወታቱን ያላሳተፈ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መዳረሻው የማይታወቅ ጉዞ ነው፡፡ በፖለቲካውም መስክ ቢሆን ያለወጣቶች ተሳትፎ ማለም ማቀድና ለውጥ ለማምጣት መሞከር ከንቱ ድካም ነው፡፡ በማህበራዊ ዘርፉም ወታቶችን በትምሀህርትና በስነ ምግባ የሚያጽ ተቋም መገንባት፤ተየንነታው የየተጠበቀ እንዲሆንና ንቁና ለአገርም ሆነ ለወገን ጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉበትን አሰራር መዘርጋት ወሳኝ ነው፡፡
ወጣት አስተዋይ አርቆ አሳቢና ለአገር ተቆርቋሪ ካልሆነ የአገር የነገ ተስፋ ሊለመልም ብልጽግናም ሆነ የለውጥ ጉዞ ሊሳካ አይችልም፡፡ ፍላጎታችንም ሆነ ትልማችን እውን እንዲሆንና የአገራችን የብልጽግና ጉዞ እንዲሳካ በወጣቱ ላይ የምንሰራው ስራ ጠንካራ መሆን አለበት፡፡
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የተካደው የወጣቶች የምከክክር መድረክ ዋነኛ ዓላማውም ይህን እሳቤ ከግቡ ማድረስ ነው፡፡